
ባሕር ዳር: ነሐሴ 12/2017 ዓ.ም (አሚኮ) መንግሥት የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞችን ጨምሮ የመንግሥት ሠራተኞችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሚያስችል አዳዲስ ማሻሻያዎችን ማድረጉን አስታውቋል።
የደመወዝ እና የግብር ማሻሻያ የተደረገባቸውም ፡-



ይህ አዲስ የደመወዝ ጭማሪ ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚኾን ሲኾን ለዚህ ማሻሻያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ስለመመደቡም ተብራርቷል። ይህም ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ የሚወጣውን አጠቃላይ ዓመታዊ ወጭ ወደ 560 ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል።መንግሥት በቀጣይ የቤት አቅርቦትን እና የጤና መድህንን ጨምሮ ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን ለማሻሻል ዕቅድ መኖሩም ነው የተገለጸው።
መንግሥት የዜጎችን ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም በተገቢው ደረጃ ለመክፈል የሚያስችል ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ጠንካራ ሥራ እየሠራ እንደሚገኝም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጠቁሟል፡፡ ይህንን ለማሳካትም የመንግሥት ሠራተኞች በየመስካቸው ውጤታማ በመኾን እና ሙስናን በመታገል የኢኮኖሚውን ዕድገት እንዲያግዙ ጥሪ ቀርቧል። ይህም የሀገርን የግብር ገቢ ለማሳደግ እና ኢኮኖሚያዊ መሠረትን ለማጠናከር ወሳኝ መኾኑ ተገልጿል።እንደ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን መረጃ መንግሥት እስካሁን ለሀገር ዕድገት እና ብልጽግና ሲሉ ዝቅተኛ ደመወዝ እየተከፈላቸው በትጋት እየሠሩ ላሉ የመንግሥት ሠራተኞች ምሥጋና አቅርቧል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን