
ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 06/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ነዳጅ በአብዛኛው ማኅበረሰብ የዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ ተፅዕኖ እያሳደረ ያለ ምርት ነው። በሀገራችን በኹሉም ዘርፍ የነዳጅ ፍላጎት በከፍተኛ መጠን እያደገ መጥቷል።
አኹን ላይ ነዳጅ ሕጋዊ ባልኾነ ቦታ ወይም አዋጁ እንዲሸጥ ባልፈቀደበት ቦታ እና ከዋጋው በላይ ሲሸጥ ይስተዋላል።
የነዳጅ ግብይትን እንዲፈጽሙ ኀላፊነት የተሰጣቸው አንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች ሳይቀር ነዳጅ እያለ የለም የሚሉበት አጋጣሚም እንዳለ በተጠቃሚዎች ይነሳል።እንደዚህ አይነት አካሄድ ከሚፈጥረው የግብይት ሚዛን መዛባት በተጨማሪ ከጋዝ ተፈጥሯዊ ባህሪ የተነሳ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል። እነዚህን እና መሰል ተግባሮችን ለመቆጣጠር አዋጁ በ2017 ዓ.ም ተሻሽሎ ወጥቷል።
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የሕግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የሕግ ባለሙያ ፍቅር በለጠ በአዲሱ የነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጅ ቁጥር 1363/2017 የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት እና ስርጭት ለመቆጣጠር የወጣ አዋጅ እንደኾነ ገልጸዋል። በዚህ አዋጅ አንቀጽ 2(1) ላይ የነዳጅ ውጤቶችን ምንነት በትርጉም ደረጃ ማስቀመጡን ይገልጻሉ። በዚሁ አንቀጽ እንደተቀመጠው “የነዳጅ ውጤቶች” ማለት የተፈጥሮ ድፍድፍ ነዳጅን፣ ፔትሮሊየም ጋዝን፣ ባዮ ፊውልን ወይም ሲንተቲክ ነዳጅን ከማጣራት ወይም ከማቀናበር የተገኘ ንፁህ ወይም አግባብ ባለው መንገድ የተደባለቀ የነዳጅ ውጤት ኾኖ ቤንዚንን፣ ኬሮሲንን፣ ናፍጣን፣ ቀላል እና ከባድ ጥቁር ናፍጣን፣ የአውሮፕላን ነዳጅን እና የመሳሰሉትን የሚያካትት ትርጉም እንደተሰጠው ያብራራሉ።
በአዋጁ አንቀፅ 2 (12) መሠረት ነዳጅ ማደያ ማለት “የነዳጅ ውጤቶችን ከአከፋፋይ ገዝቶ ለመጨረሻ ተጠቃሚዎች በችርቻሮ የሚሸጥ ሰው ነው” የሚል ትርጉም እንደተሰጠው አብራርተዋል።በዚህ ምክንያት ማንኛውም የነዳጅ ማደያ ሊያከብራቸው የሚገቡ ግዴታዎች በአዋጁ ላይ እንደተቀመጠ ይገልጻሉ።ከግዴታዎች መካከልም ማንኛውም ለሚያቋቁመው ለእያንዳንዱ የነዳጅ ማደያ በባለሥልጣኑ የሚጠየቁ መሥፈርቶችን አሟልቶ የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማግኘትን እንደሚያስገድድ አብራርተዋል።የነዳጅ ውጤቶችን ውል ከገባው አከፋፋይ ብቻ በመግዛት እና በመረከብ ነዳጅ ማደያው ውስጥ እንዲራገፍ የማድረግ ግዴታም አለበት ነው ያሉት።
የነዳጅ ውጤቶችን ከባዕድ ነገሮች ጋር ያለመቀላቀል፣ ጥራቱን ሊያጓድል ከሚችል ማናቸውም ድርጊት የመቆጠብ እና ለመጨረሻ ተጠቃሚዎች በችርቻሮ የመሸጥ ኀላፊነት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል።የዋጋ ቁጥጥር የሚደረግባቸውን የነዳጅ ውጤቶች አግባብነት ያለው የመንግሥት አካል በወሰነው ዋጋ ብቻ የመሸጥ ግዴታ አለበት ብለዋል ባለሙያዋ።ማንኛውም ማደያ ለመጨረሻ ተጠቃሚዎች ያልተቆራረጠ የ24 ሰዓት የሽያጭ አገልግሎት የመስጠት፤ ነዳጅ በማደያ ውስጥ እያለ የሽያጭ አገልግሎት ማቋረጥ እንደማይችሉም ሕጉ ያዝዛል ብለዋል።በአዋጁ የተቀመጡትን ግዴታዎች አለማክበር አሥተዳደራዊ እርምጃዎች እንደሚያስወስድ በዚኹ አዋጅ የተቀመጠ መኾኑንም ነው የሕግ ባለሙያዋ ያብራሩት።
በአዋጁ የተቀመጡትን ክልከላዎች መተላለፍ የወንጀል ተጠያቂነትንም ያስከትላል ነው ያሉት። በአዋጁ ከተቀመጡት አሥተዳደራዊ ቅጣቶች መካከል የተወሰኑትን ለማንሳት ያክል፦








በአዋጁ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች ተላልፎ ለሁለተኛ ጊዜ በመፈጸም ጥፋተኛ ኾኖ የተገኘ የግብይት ተዋናይ በዚህ አንቀጽ ከሚጣልበት ቅጣት በተጨማሪ ድርጅቱን ለአምሥት ዓመታት እንዲዘጋ የሚያስገድድ ቅጣት እንደሚጣልበት አስገንዝበዋል።
ዘጋቢ: አሰፋ ልጥገበው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን