ጣናነሽ ፪ ወደ ጣና ሐይቅ ለመግባት ዝግጁ ኾናለች።

68

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በጣና ሐይቅ ላይ ዘመናዊ የባሕር ትራንስፖርት እና የቱሪዝም አገልግሎት ለመስጠት በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋ ባሕር ዳር ከተማ የገባችው ጣናነሽ ፪ ጀልባ ዛሬ በጣና ሐይቅ ዳርቻ አርፋ ወደ ሐይቁ ለመግባት ተዘጋጅታለች።

የየብስ ጉዞዋን በኢትዮጵያውያን ፍቅር እና አንድነት ታጅባ የፈጸመችው ጣናነሽ ፪ በጣና ዳርቻ ላይ ቆማለች። ለዘመናት ውበትን፣ ታሪክን እና ሃይማኖትን ይዞ ለኖረው ጣና ሐይቅ ተጨማሪ ውበት ናት።

ጀልባዋ በቅርብ ቀን በማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ወደ ጣና ሐይቅ ገብታ አገልግሎት እንደምትሰጥም ተገልጿል።

ዘጋቢ፦ አሚናዳብ አራጋው

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

Previous article“የአረጋውያን ጧሪያቸው፣ የሕጻናት አሳዳጊያቸው”
Next articleሕዝብ እንዳይጎዳ እና እንዳይበደል በማሰብ የሰላም አማራጭ መቀበሉን የቀድሞ ታጣቂ ቴዎድሮስ ከበደ ተናገረ።