ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በሰሜን ጎንደር ደባርቅ ከተማ እየተካሄደ ነዉ።

31

ደባርቅ: መጋቢት 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በሰሜን ጎንደር ደባርቅ ከተማ እየተካሄደ ነዉ። ሕዝባዊ ሰልፉ ፈተናን በመሻገር ሰላምን ለማጽናት እና ልማትን ለማስቀጠል የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ያለመ ነው።
በድጋፍ ሰልፉ መሪ መልዕክቶች ተስተላልፈዋል። ከመልእክቶች መካከልም:-
👉ዉስጣዊ ሰላማችን በማጽናት ዉጫዊ ተጽዕኖዎችን በድል እንወጣለን!
👉 ሰላማችን በእያንዳንዳችን ቤት ናት!
👉 የክልላችን ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ እንፈልጋለን!
👉 የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድልና ስኬት የአባቶቻችን ገድል የደገምንበት ታሪካዊ አሻራ ነዉ!
👉 ኢትዮጵያ የዓድዋን ድል ዳግም እያደሰች ነዉ! የሚሉት ይገኙበታል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በደሴ ከተማ እየተካሄደ ነው።
Next articleሀገራዊ ለውጡን የሚደግፍ ሕዝባዊ ሰልፍ በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ ሀርቡ ከተማ አሥተዳደር እየተካሄደ ነው።