
በተለያዩ ክልሎች ለመከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሰልፍ እየተደረገ ነው።
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 20/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሀገርን ለማፅናት እያበረከተ ላለው አስተዋፅኦ ሕዝቡ ከጎኑ መኾኑን የሚያሳይ የድጋፍ ሰልፍ እየተደረገ ነው።
ሰልፉ በተለያዩ ከተሞች በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በኦሮሚያ፣በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በሌሎችም ክልሎች ከተሞች በጠዋቱ ወደ አደባባይ በመውጣት ለሠራዊቱ ያላቸውን ድጋፍ በሰልፍ እየገለፁ ይገኛሉ። ዘገባው የኢቢሲ እና የኢዜአ ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!