
ሰኔ 03/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በክልሎች መካከል ያለውን የእርስ በርስ ግንኙነት በማጠናከር ለሰላም፣ ለልማትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የአጎራባች ክልሎች የጋራ ፎረም አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ።
የኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ የደቡብ ምዕራብ ህዝቦችና የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች ክልል አጎራባች መንግስታት ግንኙነት ፎረም ለመመስረት የሚያስችል መድረክ በሃዋሳ አካሂደዋል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ዛሕራ ሁመድ እንዳሉት÷ ምክር ቤቱ በህዝቦች መካከል በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ ዴሞክራሲያዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ ተግባራትን እያከናወነ ነው።
ክልሎች በመካከላቸው ችግሮቻቸውን፣የልማት ሥራዎችንና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ተግባራትን በጋራ የሚያካሂዱባቸው የአጎራባች ክልሎች የጋራ መድረክ ለማቋቋም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ አለመግባባቶችን ለማስወገድ የሚረዱ ዘመናዊና ባህላዊ የግጭት መከላከያና ማስወገጃ ስልቶችን በማጥናት፣ የአሰራር ስርዓትና ስልት በመዘርጋት ተቋማዊ አደረጃጀት ለመፍጠር እየሰራ ነው ብለዋል።
አራቱ ተጎራባች ክልሎች በርካታ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ያላቸው መሆኑን የጠቆሙት ምክትል አፈ ጉባኤዋ፣ ይህ በጋራ የመኖር እሴት እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ለማሳለጥ በሚደረገው እንቅስቃሴ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት የአጎራባች ክልሎች የጋራ ፎረም አስተዋጽኦው የላቀ ነው ብለዋል።
ፎረሙ የልማት፣ የሰላም የዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በትኩረት ለማከናወን ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑንም አቶ ደስታ ገልጸዋል።
በመድረኩ የአራቱ ክልሎች የጋራ ፎረም ለመመስረት ዝግጅት የሚያደርጉ ከአራቱ ክልሎች አንድ አንድ ተወካዮችና ከፌዴሬሽን ምክር ቤት የመንግሥታት ግንኙነት የዴሞክራሲያዊ አንድነትና ንቃተ ህገ መንግሥት ቋሚ ኮሚቴ ፀሐፊ አባል የሆኑበት ኮሚቴ ተቋቁሟል።
በሲዳማ ክልል አስተናጋጅነት የሚካሄደው የመጀመሪያውን የክልሎቹ ከፍተኛ አመራሮች የጋራ መድረክ የጋራ ኮሚቴው ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ እንደሚያካሂድ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል።
#ኢትዮጵያን እናልማ፣እንገንባ፣እንዘጋጅ‼
#ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
#የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ ‼
#ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
በአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ቡድን በሰቆጣ፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ላልይበላ፣ ደሴ እና ከሚሴ አካባቢዎች የወደሙና የተዘረፉ የሚዲያ መሳሪያዎችን መልሶ በመገንባት ለሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት አሚኮን ይደግፉ።
https://ameco.bankofabyssinia.com/