“…በአንድነት ተነስተን አሸባሪዎችን ድባቅ እንመታለን” ሌተናል ጀነራል ባጫ ደበሌ

205
ሕዳር 24/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የመከላከያ ሚኒስቴር የሠራዊት ግንባታ ሥራዎች ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጀነራል ባጫ ደበሌ በጭፍራ ግንባር ተገኝተው ለሠራዊት አባላት ንግግር አድርገዋል።
በንግግራቸውም የሠራዊት አባላቱ ጀግኖች እንደሆኑ ገልፀውላቸዋል። “የምትዋጉት አሸባሪውን ብቻ ሳይሆን ጋላቢዎቻቸውን ጭምር ነው” ብለዋል።
“የውስጥ ኃይሎች ለውጪ ወኪል ሆነው ኢትዮጵያን በሚወጉበት ወቅት በአንድነት ተነስተን አሸባሪዎችን ድባቅ እንመታለን” ነው ያሉት፡፡
ይህ ትውልድ በዚህ ታሪካዊ ወቅት አሸባሪውን #የመቅበር እድል በማግኘቱ ሊደሰት ይገባል ብለዋል።
የአፋር ክልል ርእሰ መሥተዳድር አወል አርባ የአፋር ሕዝብ መከላከያን እየደገፈ ጠላትን እየመከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ወደፊትም የአፋር ሕዝብ ሽብርተኛውን እስከ መጨረሻው #ለመቅበር ሁሉንም ነገር ያደርጋል ብለዋል።
ጀግናው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ እንደተናገረው እየተዋጋችሁ ያላችሁት የአፍሪካንና የጥቁሮችን ውጊያ ነው፤ እውነትን ይዛችሁ ስለምትዋጉ ጠላትን ድል እንደምታደርጉ ጥርጥር የለኝም ሲል መግለጹን ከመከላከያ ሠራዊት የማኅበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
#መሪህን ተከተል!!
#ሀገርህን አድን!!
#ነፃነትህን አትስጥ !!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation
Previous article❝የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ በመረዳት ኢትዮጵያ ያጋጠማትን ችግር በራሷ የመፍታት አቅም እንዳላት መገንዘብ መቻላቸው ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት ነው❞ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ
Next article“ለፍትሕ፣ ለነጻነታችን፣ ለክብራችን፣ ሀገራችንን ለመጠበቅ እንፋለማለን” አቶ ተመሥገን ጥሩነህ