
የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሽጥላ ባስተላለፉት መልዕክት “የዳግማዊ ዓድዋን ታሪክ የምንፅፍበት ወሳኙ ምእራፍ ላይ ነን፤ ያለጥርጥር ደማቅ ታሪክም እንፅፋለን” ብለዋል፡፡
አቶ ግርማ በመልዕክታቸው እንዳሉት የሀገራችንን ክብር ሊደፍሩ ያሰፈሰፉ የውስጥና የውጭ ጠላቶችን አይቀጡ ቅጣት ቀጥተን የዓድዋን ታሪክ ዳግም እንፅፋዋለን። የአማራ ሕዝብም ከኢትዮጵያዊያን ወንድሞቹ ጋር ኹኖ መሪዎቹን ይከተላል፤ በወንድማማችነትና በጋራ መስዋእትነት ኢትዮጵያን ያፀናል ነው ያሉት፡፡
ያለ መስዋእትነት ድል አይገኝም!
ነፃነትህን አትስጥ!
ተዋርዶ ከመኖር በክብር መሞት ይሻላል!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ