አሸባሪው የትህነግ ወራሪ ቡድን ወረራ በፈፀመባቸው የሰሜን ወሎ የተለያዩ አካባቢዎች ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች የሰብዓዊ ድጋፎችን እንዲያቀርቡ ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ጠየቁ።

134
ደሴ: መስከረም 04/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ወሎ ዞን አሸባሪው የትህነግ ቡድን በወረራቸው የተለያዩ አካባቢዎች የሰብዓዊ ድጋፍ ባለመኖሩና የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት በመከሰቱ በርካቶች በስቃይ ውስጥ መሆናቸውን ከሰሜን ወሎ ዞን የተፈናቀሉ ወገኖች ገልጸዋል፡፡
የሽብር ቡድኑ በአቅመ ደካሞች፣ በሴቶች እና ሕጻናት ላይ በፈፀመው አሰቃቂ ግፍ ለሞት መዳረጋቸውንና በሕይወት የተረፉትም በርሃብ እና በመድኃኒት እጥረት ምክንያት በችግር ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡
ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች በአካባቢዎቹ በመግባት የሰብዓዊ ድጋፎችን እንዲያቀርቡ ጠይቀዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ቤተልሄም ሰለሞን
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleአሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን የአቅመ ደካሞችን ቀለብ ሳይቀር ዘረፋ መፈጸሙን የገረገራ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
Next articleኢትዮጵያን በውጭ የሚወክሏት ሚሲዮኖች በአዲስ መልኩ ሊዋቀሩ ነው፡፡