የተከዜን ኮሪደር ተገን ያደረገው የጠላት ጦር በአካባቢው የሚሊሻ አባላት ተደመሰሰ፡፡

292

ሰቆጣ፡ ነሐሴ 28/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ሰሃላ ሰይምትን እና ዝቋላን በሚያካልለው የተከዜ ወንዝ ኮሪደር ተገን አድርጎ አካባቢውን ሲዘርፍ የነበረው የአሸባሪው ትህነግ ቡድን አባላት በአካባቢው ሚሊሻ ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል፡፡

የአሸባሪው ትህነግ ቡድን አባላት ተሸከርካሪዎችን ጨምሮ በስሃላ ሰየምት እና ዝቋላ አካባቢ የዘረፉትን ሃብት እና ንብረት ወደትግራይ ለማሸሽ ጥረት ላይ እያሉ በድንበር አካባቢዎች መሽጎ የነበረው የአካባቢው የሚሊሻ አባላት እና ወጣቶች ሙሉ በሙሉ ደምስሰውታል፡፡

ከስሃላ ሰየምት ተባሮ ወደ ዝቋላ የገባውን የአሸባሪ ቡድን በመደምሰስ የምዕራብ እና የምስራቅ በለሳ ሚሊሻዎች ተሳትፈዋል ተብሏል፡፡

የሰሃላ ሰየምት እና ዝቋላ ወረዳዎችም ከአሸባሪ ቡድኑ በማስለቀቅ በአካባቢው የሚሊሻ አባላት ቁጥጥር ስር ገብተዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ከፍያለው ደባሽ -ከስሃላ ሰየምት

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleምሽት 12:00 ዜና ሙዳይ ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 28/2013 ዓ.ም (አሚኮ)
Next articleአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በአረብኛ ቋንቋ ሥርጭት መክፈቱ ተገቢ ውሳኔ ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የአልጀዚራ ኀላፊ መሀመድ ተዋከል ገለጹ፡፡