ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ የተላለፈ መልዕክት

258

ለስግብግቡ ጁንታ ግፍ እስትንፋሱ፣ ጭካኔ ነፍሱ ነው። ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ሽራሮን ሲቆጣጠር፣ እጅና እግራቸውን የፊጥኝ ታሥረው የተረሸኑ የመከላከያ አባላትን አግኝቷል። ጭካኔው ልብ ሰባሪ ነበር። ዓላማው ኢትዮጵያን መስበር ነው። አላወቁም ከአልማዝ የጠነከረች መሆኗን። ዓላማው ሠራዊታችንንና ሕዝቡን አስቆጥቶ ለበቀል ርምጃ ማነሣሣት ነው። አላወቁም ልበ ሰፊ ሕዝብና ሠራዊት እንዳለን።

በየቦታው ስንደርስ ከዚህ የከፋ ጭካኔና ግፍ ሊገጥመን ይችላል። ይህ ግን ለዚህ ጁንታ የመጨረሻው ነው። ጥንቃቄያችን ‘ሙት ይዞን እንዳይሞት’ ነው። መፍጠን አለብን፤ የተረፉትን ለመታደግና ግፍ የተፈጸመባቸውንም ለዓለም ለማጋለጥ።

የምዕራቡን የትግራይ ክልል ቀጣና ነጻ ወጥቷል። በዚያ ቀጣና ሠራዊቱ ሰብዓዊ ርዳታና አገልግሎት እየሰጠ ነው። ነጻ ባወጣቸው አካባቢዎች ሕዝቡን እየመገበ፣ እያከመና እየተንከባከበ ነው።

Previous articleየኢትዮጵያ እና የጀርመን ወታደራዊ ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ጉብኝት በሁርሶ ኮንቲጀት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ተካሄደ፡፡
Next articleበኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያልተረጋገጠ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አሳሰበ፡፡