የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) እና ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) የሚተላለፉ ውሳኔዎችን በመቀበል በተግባር እያዋለ ይገኛል።
በዚህም መሰረት በሚቀጥለው የውድድር ዓመት በኢትዮጵያ ሴቶች ሊግ ላይ ለሚሳተፉ ክለቦች አዲስ እና አስገዳጅ መመሪያ አጽድቋል።
መመሪያው ክህሎት እያላቸው ዕድል ላጡ ሴት አሠልጣኞች ሰፊ የሥራ በር የሚከፍት ነው።
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሴቶች ልማት ዴስክ ኀላፊ በኃይሏ ዘለቀ እንዳሉት ይህ ውሳኔ በየጊዜው የሙያ ፈቃድ ሥልጠና እየወሰዱ ወደ ጎን የተገለሉ እና ዕውቀት ያላቸው አዳዲስ አሠልጣኞችን የምናገኝበት ይኾናል ብለዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ይህንን የወጣውን አዲስ መመሪያ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቋል።
#ባሕር_ዳር፡ ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም
ዘጋቢ:
ዳናይት ሲሳይ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!



