ባሕር ዳር: ሚያዝያ 07/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በኢትዮጵያ ፕሪምዬር ሊግ 27ኛ ሳምንት ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ።
ዛሬ ከሚደረጉ ጨዋታዎች መካከል ኢትዮጵያ መድን ከባሕር ዳር ከተማ ቀን 9፡00 ላይ በአዲስ አበባ አበበ ቢቄላ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ አንዱ ነው።
በ26ኛ ሳምንት አዳማ ከተማን ያሸነፈው ባሕርዳር ከተማ የዛሬውን ጨዋታ በጥሩ የማሽነፍ ስነ ልቦና እንደሚያደርገው ይጠበቃል።
፡ሀዋሳ ከተማ እና የሽረ ምድረ ገነት ጨዋታ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9:00 ይካሄዳል።
በሌላ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ከመቻል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምሽት 12፡00 ላይ ይጫወታሉ።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



