በቶኪዮ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል።

0
220

ባሕር ዳር: የካቲት 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የቶኪዮ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል። በወንዶች ታደሰ ታከለ ሲያሸንፍ በሴቶች ደግሞ አትሌት ሱቱሜ አሰፋ አሸንፋለች።

በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው በዚህ ማራቶን በሴቶች አትሌት ሱቱሜ አሰፋ 2 ሰዓት ከ16 ደቂቃ ከ31ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች ።

በወንዶች ደግሞ አትሌት ታደሰ ታከለ በ2 ሰዓት ከ3 ደቂቃ 23 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት የግል ምርጥ ሰዓቱን ጭምር በማሻሻል አሸንፏል።

አትሌት ደረሳ ገለታም ሁለተኛ ደረጃ ይዞ እንዳጠናቀቀ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አሳውቋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here