ማንቸስተር ዩናይትድ እና ብራይተን የካሜሩናዊውን አማካይ ካርሎ ባሌባን ዝውውር በተመለከተ ስምምነት ላይ ለመድረስ ከፍ ያለ ውይይት እያደረጉ መሆናቸውን የ”ዘ አትሌቲኩ” ጋዜጠኛ ዴቪድ ኦርንስቴይን ዘግቧል።

0
5
ለ22 ዓመቱ ተጫዋች ዩናይትድ 60 ሚሊዮን ፓውንድ ከ ተጨማሪ 5 ሚሊዮን ፓውንድ (add-ons) ያቀረበ ቢሆንም፣ ብራይተን ከዚህ ከፍ ያለ ዋጋ እንደሚሻ ይገመታል።
ባሌባ በአሁኑ ወቅት በቁርጭምጭሚት ጉዳት ምክንያት ከሜዳ የራቀ ቢሆንም፣ ጉዳቱ ለረጅም ጊዜ የሚያቆየው አሳሳቢ ችግር አይደለም።
ዩናይትድ በዚህ ክረምት ዩሪ ቲሌማንስን እና አንድሬ ሳንቶስን ያስፈረመ ሲሆን፣ የካርሎ ባሌባ ዝውውር ከተሳካ ከኮቢ ማይኑ እና ከብሩኖ ፈርናንዴዝ ጋር በመሆን በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ስር የአማካይ ክፍሉን የበለጠ አጠናክሮ ይቀጥላል።
ባሌባ ከፈረንሳዩ ሊል ክለብ በ2023 ወደ ብራይተን ከተቀላቀለ ወዲህ በድምሩ 112 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን፣ ሁለቱም ክለቦች ስምምነት ላይ ለመድረስ አሁን የሚፈጸም የሚመስል ውይይቶችን እያደረጉ ይገኛሉ።
ጥበቡ ሰለሞን
#ባሕር_ዳር፡ ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here