ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው።

123

ባሕር ዳር፡ መስከረም 22/2013ዓ.ም (አብመድ) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ባለቤታቸው ሜላኒያ ትራምፕ በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ይህን ያሳወቁት እራሳቸው ፕሬዝዳንት ትራምፕ በማኅበራዊ ገጻቸው ነው።
“ዛሬ በኮሮናቫይረስ መያዛችን ተረጋግጧል፤ ለብቻችን ሆነን የምናገግም ይሆናል” ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

የፕሬዝዳንቱ የቅርብ ሰው ሆፕ ሂክስ ቀደም ብሎ በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ትራምፕና ባለቤታቸው ራሳቸውን አግልለው ነበር ያለው ደግሞ ሲ ኤን ኤን ነው።

ትራምፕ የኮሮናቫይረስን ማጣጣላቸውና ተገቢውን ትኩረት አለመስጠታቸው ሲያስወቅሳቸው ነበር።

Previous articleበክፍለ ከተማው ያሉ ተወላጆችን በማስተባበር የላቀ ድጋፍ ለማግኜት እየሠራ መሆኑን አልማ አስታወቀ።
Next articleየቲሊሊ ከተማና አካባቢው ኅብረተሰብ ኪሊ መስክ ትምህርት ቤትን በአዲስ ገነቡ፡፡