በልደታ ክፍለ ከተማ ከ35 ሺህ ብር በላይ ነባሩ ባለሃምሳ ሐሰተኛ የብር ኖት ከነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡

640

ባሕር ዳር፡ መስከረም 21/2013ዓ.ም (አብመድ) በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ከ35 ሺህ ብር በላይ ነባሩ ባለሃምሳ ሐሰተኛ የብር ኖት ከነተጠርጣሪው ተይዞ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ፡፡
የአዲስ አበባ እና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አባላት ከጥርጣሬ በመነሳት በአንድ ግለሰብ ላይ ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ በእጅ ቦርሳው ውስጥ 35 ሺህ 50 የቀድሞውን ባለሃምሳ ሐሰተኛ የብር ኖት ከአንድ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ቲተር ጋር ከእነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር አውለዋል ብሏል ኮሚሽኑ፡፡

የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች መርማሪ ምክትል ሳጅን ንጉሴ ማናዬ ኅብረተሰቡ ግብይት በሚፈጽምበት ወቅት በሐሰተኛ የብር ኖቶች የማታለል ወንጀል እንዳይፈጸምበት መለያዎቹን በጥንቃቄ በመመልከት እንዲገበያይ እና አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ ማሳሰባቸውን ኢብኮ ዘግቧል፡፡

Previous article“ከመስከረም 30 በኋላ መንግሥት የለም እያሉ ለሚያወዛግቡ ኃይሎች የአማራ ክልል መንግሥትና ሕዝብ ቦታ እንደማይሰጡ ርእሰ መሥተዳድሩ አስታወቁ።
Next articleየኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ፡፡