የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ከ 97 ሚሊዮን ብር በላይ ውዝፍ እዳ ለጎንደር ከተማ አስተዳደር እንዲከፍል የፍርድ ቤት ውሳኔ ተላለፈ።

221

ድርጅቱ ለአውሮፕላን ማረፊያና ለቢሮ አገልግሎት ከ2002 ዓ·ም እስከ 2012 ዓ·ም ድረስ ሲጠቀምበት ለነበረው ቦታ 97 ሚሊዮን 584 ሺኅ 125 ብር እንዲከፍል በፍርድ ቤት ተወስኖበታል።

የኢትዮጵያ ኤርፓርቶች ድርጅት የጎንደር አፄ ቴዎድሮስ ኤርፖርት አስተዳደር ለ10 ዓመታት የተጠቀመበትን የቦታ ኪራይ ውዝፍ እዳ ነው እንዲከፍል የተወሰነበት።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከተማ ነክ ጉዳዮች የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ድርጅቱ የቦታ ክራይ አለመክፈሉን በማረጋገጡ ለተጠቀመበት ቦታ በግብር ህጉ ስሌት መሠረት እንዲከፍል መወሰኑን ከከተማ አስተዳደሩ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

Previous articleየኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ከ 97 ሚሊዮን ብር በላይ ውዝፍ እዳ ለጎንደር ከተማ አስተዳደር እንዲከፍል የፍርድ ቤት ውሳኔ ተላለፈ።
Next articleሦስት ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ የታቀደበት ‘’ገበታ ለሃገር’’ ይፋ ተደረገ።