
ወልድያ: መጋቢት 29/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ዕለተ ማክሰኞ የሰሜን ወሎ ዞን እና የአጎራባች ክልል ነዋሪዎች ወልድያ ገበያ ላይ ሽያጭ እና ግዥ የሚያከናውኑበት ቀን ነው።
የወልድያ ማክሰኞ ገበያ ማኅበራዊ መስተጋብር የሚጠናከርበት፤ የተነፋፈቀ የሚገናኝበት ተናፋቂም ነው።
ይህ ገበያ:-
“ማክሰኞ ወልድያ ሰኞ ቆቦ ዋልኩኝ፤
የሸጋ ልጅ ጠረን እየተከተልኩኝ፤
ልሂድ በወልድያ በአዋጅ መንገሪያው
ማክሰኞ ገበያ ሰው መገናኛው” እየተባለ ተገጥሞለታል።
አሚኮ የትንሣኤ በዓል ግብይትን በሳምንታዊው ማክሰኞ ገበያ ተገኝቶ ቃኝቷል።
የእርድ እንስሳት በቂ አቅርቦት ቢኖርም ከልደት ገበያ ጋር ሲነጻጸር አንጻራዊ ጭማሪ ማሳየቱን ሸማቾች ነግረውናል።
የወልድያ ከተማ አሥተዳደር እንስሳት እና ዓሳ ሃብት ልማት መምሪያ ኀላፊ በላይ ገሰሰ የእርድ እንስሳት አቅርቦት እጥረት እንዳይኖር መሠራቱን ተናግረዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
