አቢሲኒያ ባንክ በ”ይጀምሩ ያድሱ ይደጉ” መርሐግብሩ አዳዲስ ደንበኞች ማፍራቱን ገለጸ።

10
አዲስ አበባ፡ የካቲት 19/2018 ዓ.ም (አሚኮ) አቢሲኒያ ባንክ ለሁለት ወራት ሲያካሂድ የቆየው “ይጀምሩ ያድሱ ይደጉ” መርሐ ግብር መጠናቀቁን አስመልክቶ የዕጣ ማውጣት ሥነ ሥርዓት አከናውኗል።
በመርሐ ግብሩ 11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ደንበኞችን በማካተት ለ22 ዕጣዎች በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዕጣ እንዲወጣ አድርጓል።
የባንኩ የደንበኞች ችፍ ኤክስኩቲቭ ማኔጀር ደሳለኝ ዘርጋው ይጀምሩ ያድሱ ይደጉ” መርሐ ግብር ዋና ዓላማው አዳዲስ ደንበኞችን ማፍራት፣ የተቀማጭ ገንዘብን እና የዲጂታል ደንበኛን ማሳደግ እና ወረቀት አልባ አገልግሎትን ማጠናከር ነው ብለዋል።
በዚህም 258ሺህ አዳዲስ ደንበኞች አፍርቷል። ከ140 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ በማግኘትም 11 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ መሠብሠብ ተችሏል ብለዋል። 33 ሺህ የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ መፍጠር መቻሉንም ጠቅሰዋል።
በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የተለዩ ከ11 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች በዕድል ዕጣው ተካትተው 22 ዕድለኞችም ተለይተዋል።
ሀዩንዳይ መኪና፣ ሦሥት ላፕቶፕ፣ ሦሥት የልብስ ማጠቢያ ማሽን እና ሌሎች 15 ሽልማቶች ዕጣቸው ወጥቷል።
በሴንትራል አዲስ ዲስትሪክት የፍልውኃ ቅርንጫፍ ደንበኛው እድለኛም በአንደኛ ዕጣ የቤት መኪና ባለቤት መኾን ችሏል።
ዘጋቢ፦አንዱዓለም መናን
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየኮሪደር ልማት ከውበት ባሻገር
Next articleየስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክን አስፍቶ እና አጠናክሮ እንደ አዲስ በዩኔስኮ ለማስመዝገብ እየተሠራ ነው።