ምርጫውን ነጻ እና ተአማኒ ለማድረግ እየተሠራ ነው።

4
ደባርቅ፡ የካቲት 19/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የሰሜን ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የማኔፌስቶ እና የምርጫ መለያ ምልክት ትውውቅ አካሂዷል።
በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል የርእሰ መሥተዳድሩ የጸጥታ ጉዳዮች አማካሪ ዘላለም ልጃለም (ዶ.ር) መንግሥት ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ነጻ እና ተአማኒ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሠራ ነው ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት በከተማ እና በገጠር ያለውን ማኅበረሰብ በጋራ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል።
በቀጣይም የኢትዮጵያን የባሕር በር ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ይሠራል ነው ያሉት።
የፓርቲው የምርጫ ምልክት የኾነው የስንዴ ነዶ የአንድነት፣ የመተሳሰብ እና ከተረጅነት ነጻ በመውጣት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ብርቱ ጥረት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የሰሜን ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አደራጀው ባዘዘው በተለያዩ የልማት ዘርፎች በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸዋል።
በተከናወኑ ተግባራትም የማኅበረሰቡን ኑሮ በማሻሻል እና የሀገርን ኢኮኖሚ በማሳደግ በኩል ለውጥ ማምጣት መቻሉንም ተናግረዋል።
በቀጣይ ጊዜያትም የሀገርን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እና የማኅበረሰቡን ኑሮ ማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራትን ማዕከል ተደርጎ እንደሚሠራ አስገንዝበዋል።
የሰሜን ጎንደር ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ እና የትምህርት መምሪያ ኀላፊ ክቡር አሰፋ ብልጽግና ፓርቲ በሀገረ መንግሥት ግንባታ የጸና የዴሞክራሲ ሥርዓትን በመፍጠር ተስፋ ሰጭ ተግባራትን አከናውኗል ብለዋል።
በዲፕሎማሲው ዘርፍ የውጭ ጉዳይን በማጠናከር የዘመናት ጥያቄ የነበረውን የባሕር በር ጥያቄ ለመፍታት በትኩረት እየተሠራ መኾኑን አንስተዋል።
በቀጣይ በሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማኅበረሰቡ በነጻነት ድምጹን እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleበአማራ ክልል አራት ሞዴል ትምህርት ቤቶች እየተገነቡ ነው።
Next articleየአትላንቲክ ኢኒሼቲቭ እና የኢትዮጵያ የባሕር በር የመሻት ጉዳይ