
ባሕር ዳር፡ የካቲት 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በኢትዮጵያ በርካታ እናቶች የማህጸን መውጣት ችግር አጋጥሟቸው ለረጅም ዓመታት በስውር ሕመም እንደሚሰቃዩ ይነገራል። ይሁን እንጂ ባለሙያዎች ችግሩ ቀድሞ ከተለየ በቀላሉ በሕክምና ሊድን የሚችል መኾኑን በመግለጽ እናቶች ሕመማቸውን ደብቀው መቆየት እንደማይገባቸው ይገልጻሉ።
የማህጸን መውጣት ምንድን ነው? መንስኤዎቹስ?
እንደ ማህጸን እና ጽንስ ስፔሻሊስት ዶክተር በላይነው ቀለብ ማብራሪያ፣ የማህጸን መውጣት ማለት ማህጸን እና በአካባቢው ያሉ አካላት ደጋፊ ጡንቻዎቻቸው በመላላታቸው ምክንያት ወደ ታች መንሸራተት ወይም መውረድ ማለት ነው።
ዋና ዋና አጋላጭ ምክንያቶች፦
ምልክቶቹ ምንድን ናቸው?
እናቶች የሚከተሉት ምልክቶች ሲታዩባቸው በፍጥነት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይኖርባቸዋል፦
የሕክምና አማራጮች
ሕክምናው እንደ ሕመሙ ደረጃ እና እንደ እናቶች ፍላጎት ይወሰናል፦
ችግሩ ቀለል ያለ ሲኾን የሰውነት ክብደትን መቀነስ፣ የሆድ ድርቀትን መከላከል እና የዳሌ ጡንቻዎችን የሚያጠናክሩ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ይገባል።
ከባድ ደረጃ ላይ በተለይም በቀዶ ጥገና የሚሠራበት ጀረጃ ላይ ሲደርስ ደግሞ ወደፊት ልጅ መውለድ ለሚፈልጉ እናቶች ማህጸንን ወደ ቦታው የመመለስ፣ ለሌሎች ደግሞ እንደ አስፈላጊነቱ ማህጸንን ሙሉ በሙሉ የማስወገድ ሕክምና ይሰጣል።
የመከላከያ መንገዶች
የማህጸን እና ጽንስ ስፔሻሊስት ዶክተር በላይነው ቀለብ እናቶች በጤና ተቋም እንዲወልዱ፣ ከወሊድ በኋላ የሰውነት እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ፣ በፋይበር የበለጸጉ ምግቦችን በመመገብ ድርቀትን እንዲከላከሉ እና ከባድ ሸክሞችን እንዲቀንሱ መክረዋል።
ችግሩ “የፈጣሪ ቁጣ ወይም እርግማን አይደለም” የሕክምና ባለሙያው እናቶች ሳይፈሩ እና ሳይደብቁ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድ ጤንነታቸውን እንዲመልሱም አሳስበዋል።
ዘጋቢ፦ ሰናይት በየነ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
