
ደብረ ብርሃን: የካቲት 05/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር 1 ቢሊዮን ብር ካፒታል ወጭ የተደረገባቸው አራት ኢንዱስትሪዎች የክልል እና የዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት የምረቃ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።
ከሚመረቁት ውስጥ በጫጫ ክፍለ ከተማ በ152 ሚሊዮን ብር ወደ ሥራ የገባው አክሊሉ ክብረት የፕላስቲክ ውጤቶች ማምረቻ ለ120 ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረ ነው።
ሌሎች የምስር ማቀነባበሪያ፣ የፕላስቲክ እና የጫማ ማምረቻ ፋብሪካዎችም ዛሬ ይመረቃሉ።
ዘጋቢ:- በላይ ተስፍዬ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
