
ባሕር ዳር፡ ጥር 27/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል የሴቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ፎረም ምሥረታ ሥነ ሥርዓት ላይ የክልል ባለድርሻ አካላት እና የዞን የሴቶች አደረጃጀት መሪዎች ተገኝተዋል።
የፎረሙ መመሥረት በየደረጃው የሚገኙ ሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድግ መኾኑ ተገልጿል።
አደረጃጀቱን በማጠናከርም የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሠራ ነው በመድረኩ የተብራራው።
ዘጋቢ፦ ዋሴ ባየ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
