
ባሕር ዳር: ጥር 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የቅዱስ መርቆሬዎስ ዓመታዊ የንግሥ በዓል በእስቴ ዴንሳ ተራራ ግርጌ በአምቦ ሜዳ በድምቀት እየተከበረ ነው።
በክብረ በዓሉ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል። የፈረስ ጉግስ ትርኢት የበዓሉ ድምቀት ነው።
ከመካነ ኢየሱስ ከተማ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው በዓሉ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን እና ባሕላዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት እየተከበረ ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
