
ባሕር ዳር: ጥር 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ)በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አሥተዳደር ሕወሃት የሚያደርገውን ትንኮሳ የሚቃወም ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ሕዝብ ላይ በደል ሲያደርስ የኖረው የሕወሃት ቡድን ከሰሞኑ በጠለምት እና በሌሎች አካባቢዎች ትንኮሳ መፈጸሙ ይታወሳል። የወልቃይት ጠገዴ ሰቱት ሁመራ አማራ ሕዝብም ይሄን ትንኮሳ ለመቃወም እና ከመንግሥት ጎን በመኾን ሰላምን ለማረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት ለመግለጽ ሰላማዊ ሰልፍ እያካሄደ ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
