
ባሕር ዳር: ጥር 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ)የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በተገኙበት 10ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ጥር 26/2018 ዓ.ም ያካሂዳል።
ምክር ቤቱ በነገው ስብሰባው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች የሚሰጡትን ምላሽና ማብራሪያ እንደሚያዳምጥ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
