በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለመጠገን በተወሰዱ እርምጃዎች አበረታች ውጤት ተገኝቷል።

13
እንጅባራ: ጥር 18/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአዊ ብሔረሰብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 34ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።
የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ሙሉዓዳም እጅጉ ባለፉት ስድስት ወራት በሰላም እጦት ምክንያት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለመጠገን የተወሰዱ እርምጃዎች አበረታች መኾናቸውን ገልጸዋል።
ዘርፉ ሙሉ በሙሉ ከችግሩ እንዲወጣ በየደረጃው ያሉ የምክር ቤት አባላት ተግባሩን በትኩረት በመያዝ መፈጸም እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል።
በብሔረሰብ አሥተዳደሩ በሁሉም ዘርፍ የተመዘገቡ በርካታ ስኬቶች የመኖራቸውን ያህል ዛሬም የመሪዎችን ቁርጠኝነት የሚሹ ተግባራት መኖራቸውን ተናግረዋል።
የግብርና ሥራን ለማዘመን የተጀመሩ ሥራዎችን ማስፋት፤ ሥራ አጥነትን መቀነስ እና የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች መኾናቸውንም አንስተዋል።
በተቋማት የሚሰጠው አገልግሎት ወቅቱን የሚመጥን፤ የዜጎችን እንግልት የሚቀንስ፤ ጊዜን፣ ጉልበትን እና ገንዘብን ቆጣቢ መኾን ይገባልም ነው ያሉት። እያደገ የመጣውን የልማት ፍላጎት ለመመለስ የገቢ አሰባሰብ አቅም ማሳደግ እንደሚገባም አንስተዋል።
በብሔረሰብ አሥተዳደሩ እየታየ ያለውን አንጻራዊ ሰላም ለማጽናት ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ወገኖች የሰላም አማራጭ እንዲከተሉ ግፊት ማድረግ ያስፈልጋልም ብለዋል።
ምክር ቤቱ በአንድ ቀን ውሎው የባሕል ቱሪዝም እና ስፖርት መምሪያ እና የከፍተኛ ፍርድ ቤት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን ገምግሞ በማጽደቅ እና የተጓደሉ የአሥፈጻሚ ተቋማትን ሹመት በማጽደቅ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ:- ሳሙኤል አማረ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየተደረገውን የሰላም ስምምነት የተቀበሉ የአፋሕድ መሪዎች እና አባላት በጎንደር ከተማ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።
Next articleየግብርና ግብዓቶች ቁጥጥር ካልተደረገባቸው ከፍተኛ ውድመት ሊያስከትሉ ይችላሉ።