በክልሉ መንግሥት እና አፋሕድ መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በታች ጋይንት ወረዳ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ወደ ሰላም ገቡ።

83
ባሕር ዳር: ጥር 15/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በደቡብ ጎንደር ዞን ታች ጋይንት ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በርካታ ቁጥር ያላቸው ታጣቂዎች ከነሙሉ ትጥቃቸው የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ገብተዋል።
የሰላም ጥሪውን ተቀብለው የመጡ ታጣቂዎችን የ10ኛ ዕዝ ክፍለ ጦር አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል አሰጋ አከለ እና የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርታ ጽህፈት ቤት ኀላፊ መንበረ ክፈተው፣ የሃይማኖት አባቶች እና የወረዳው መሪዎች ተቀብለዋቸዋል።
ሌተናል ኮሎኔል አሰጋ አከለ ሰላምን የመረጡ የቡድኑ አባላት ስህተታቸው ገብቷቸው ሕዝባቸውን ይቅርታ ጠይቀው በመመለስ ነገ ከመንግሥት ጎን ኾነው ሀገራቸውን ለማገልገል መወሰናቸው ተገቢ ነው ብለዋል።
የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ መንበረ ክፈተው በዞኑ ግዳጁን እየተወጣ ያለው መከላከያ ሠራዊት የሚያደርገው ተደጋጋሚ ስምሪት እና የተደረጉ ውይይቶች ታጣቂዎች በሰላም እንዲገቡ ማገዙን መናገራቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleከግጭት ወጥቶ ጊዜን ለልማት ማዋል እንደሚገባ የአፋሕድ መሪዎች ተናገሩ።
Next article“የሰላም ስምምነቱ የታጣቂዎችን አመለካከት የቀየረ ነው” ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ