
ባሕር ዳር: ጥር 14/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የጥርን በባሕር ዳር መርሐ ግብር በተለያዩ ክንውኖች ቀጥሏል። የመርሐ ግብሩ አካል የኾነው የታንኳ ቀዘፋ ውድድር በጣና ሐይቅ መካሔድ ጀምሯል።
በውድድሩ በቀደምት አባቶቻችን በባሕላዊ መንገድ ከደንገል የተሠራውን ታንኳ በመጠቀም ነው ውድድሩ የሚካሄደው።
ይህ የታንኳ ቀዘፋ ውድድር በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቅ ልዩ የባሕር ዳር እና የጣና ሐይቅ ጌጥ ነው። ተወዳዳሪዎች ከባሕር ዳር እና አካባቢዋ የመጡ ናቸው።
ዘጋቢ:- አሰፋ ልጥገበው
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
