
ባሕር ዳር: ጥር 01/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80 ዓመታት የስኬት ጉዞ አለው። የአዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በዓመት 25 ሚሊዮን ተጓዦችን በማስተናገድ በእጅጉ ተጨናንቋል።
በ160 በላይ ዘመናዊ አውሮፕላኖች (በቅርቡ 60 አዲስ አውሮፕላኖች ይጨመራሉ) ወደ 145 በላይ መዳረሻዎች መብረር ሲታሰብ አንድ አውሮፕላን ጣቢያ እንደማይበቃ ግልጽ ይኾናል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ስለዚህም ተጨማሪ ማረፊያ መሥራት ይገባል ነው የተባለው። ትልቅ ታሪክ፤ የላቀ ትስስር፤ የላቀ እቅድ።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
