ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ መቀበላቸውን ቀጥለዋል።

36
ባሕር ዳር: ጥር 01/2018 ዓ.ም (አሚኮ)በደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለው ገብተዋል።
የሰላም አማራጭን የተቀበሉት ታጣቂዎች በወረዳው ወለላ ባሕር ቀጣና ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ናቸው። በአካባቢው በጫካ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን እየተቀበሉ መግባታቸውን ቀጥለዋል።
ከላይ ጋይንት ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው የሰላም አማራጭን የተቀበሉትን ታጣቂዎች በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የሀገር መከላከያ ሠራዊት መሪዎች እና የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየገታራ በራራ በሽሎ ወንዝ አሞር ገደል መሻገሪያ ተንጠልጣይ ድልድይ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት ኾነ።
Next articleግጭትን አውግዘዋል፤ ለሰላም ተነስተዋል!