በጃቢ ጠህናን ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀበሉ።

78
ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በምዕራብ ጎጃም ዞን በጃቢ ጠህናን ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለው ገብተዋል።
ታጣቂዎቹ የአማራን ሕዝብ ነጻ እናወጣለን በሚል ወደ ጫካ ገብተን በሕዝባችን ላይ የሰላም እጦት እንዲከሰት ምክንያት ኾነናል ብለዋል። የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ እና ለማገልገል የሰላምን አማራጭ መቀበላቸውንም ገልጸዋል።
ከምዕራብ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ሌሎች ታጣቂዎችም የሰላም አማራጭ እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleደሴ ከተማ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የልማቱ ተቋዳሽ እየኾነች መጥታለች።
Next articleየአገው ፈረሰኞች በዓልን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እየተደረገ ነው።