በደሴ ከተማ የተነሳ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ከ86 በላይ የቤተሰብ አስተዳዳሪዎችን ለጉዳት ዳረገ፡፡

162

በከተማዋ ጅብሩክ እየተባለ በሚጠራው ጥንታዊ ስፍራ የተከሰተው የእሳት አደጋ በአካባቢው የነበሩ ሱቆችን ሙሉ በሙሉ አውድሟል፡፡ ነጋዴዎቹ ልብስ በመስፋት ስራ ላይ የተሰማሩ ነበሩ፤ በአንድ ሱቅ ውስጥም ከአንድ እስከ አራት የልብስ ስፌት ማሽኖች ይገኙ እንደነበር ተጎጂ ነጋዴዎቹ ገልፀዋል፡፡

የከተማዋ ወጣቶች ተጎጅዎችን ለመደገፍ የሚያስችል ገንዘብ ማሰባሰብ ሥራን በህጋዊ መንገድ እንደጀመሩም ታውቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ የሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን ዋና ክፍል ኃላፊ ኮማንደር ከበደ በሽር እንደገለፁት በስፍራው ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን አና የእሳት አደጋውን መንስኤ በመጣራት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ተጎጂዎችን በዘላቂነት ለመደገፍም ሁሉም መረባረብ እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ዘጋቢ፦ሕይወት አስማማው

Previous articleበአማራ ክልል በ 24 ሰዓታት የኮሮናቫይረስ ምርመራ የተደረገላቸው ሁሉም ከቫይረሱ ነጻ ሆነዋል፡፡
Next articleበጋዜጠኞች እና በጋዜጠኝነት ሙያ ያለውን ጫና ማስቀረትና ዘርፉን ማጎልበት ላይ ጠንክሮ እንደሚሠራ የኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች ማኅበር አስታወቀ።