
ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 12/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ሰዓት በደሴ እና አካበቢዋ ባለው ለበረራ አመቺ ያልሆነ የአየር ፀባይ ምክንያት በዛሬው እና በነገው ዕለት ወደ ከተማዋ የሚያደርገውን በረራ ለማቋረጥ መገደዱን አሳውቋል።
ከሚቲዎሮሎጂ በሚገኘው መረጃ መሰረት የአየር ፀባዩ እንደተስተካከለ በረራዎቹ ወደ መደበኛ አገልግሎታቸው የሚመለሱበትን ጊዜ እንደሚያሳውቅ አየር መንገዱ ገልጿል። በአገልግሎቱ መቋረጥ ለሚፈጠሩ መጉላላቶችም ከወዲሁ ይቅርታ ለመጠየቅ እንወዳለን ብሏል አየር መንገዱ።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
