በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓታት የኮሮናቫይረስ የናሙና ምርመራ የተደረገላቸው ሁሉም ከቫይረሱ ነጻ ሆነዋል፡፡

162

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓታት ለ462 ናሙናዎች ምርመራ ተደርጎ ሁሉም ሰዎች ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ አረጋግጧል፡፡

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ እንዳስታወቀው ባለፉት 24 ሰዓታት ከቫይረሱ ያገገመ፣ ወደ ጽኑ ህሙማን ህክምና ክፍል የገባም ሆነ በቫይረሱ ምክንያት ህይወቱ ያለፈ የለም፡፡

በአማራ ክልል እስከ ዛሬ ሰኔ 17/2012 ዓ.ም ድረስ ለ11 ሺህ 880 ሰዎች የናሙና ምርመራ ተደርጎ በ277 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል፡፡

ቫይረሱ ተገኝቶባቸው በለይቶ ሕክምና መስጫ ማዕከላት የሚገኙ ሁሉም ታካሚዎች በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙም ቢሮው አስታውቋል፡፡

እስከዛሬ በክልሉ 84 ሰዎች ከቫይረሱ አገግመዋል፤ ሁለት ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ምክንያት ሕይወታቸውን አጥተዋል፡፡

በደጀኔ በቀለ

Previous articleአዋጁ በትክክል እንዲተገበር እና የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀረበ፡፡
Next articleየታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ የበይነ መረብ ዘመቻ ሊካሄድ ነው።