
ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 04/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የክልል እና የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ መሪዎች “የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች” በሚል መሪ መልዕክት በወቅታዊ ክልላዊ እና አካባቢያዊ ጉዳዮች ዙሪያ በደሴ ከተማ ከልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት እያደረጉ ነው።
የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አወሉ አብዲ፣ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኀላፊ ፍስሀ ደሳለኝ፣ የከተማ አሥተዳደሩ እና የዞኑ መሪዎች በመድረኩ ተገኝተዋል።
የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች እና ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ተወካዮች በውይይቱ እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፦ አሚናዳብ አራጋው
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
