የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኀይል ንቅናቄ (አዴኀን) 3ኛውን ድርጅታዊ መደበኛ ጉባኤ ጀምፘል።

16
ባሕር ዳር: ሕዳር 28/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በመደበኛ ጉባኤው ከሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የተወከሉ ጉባኤተኞች የተሳተፉ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጭ ቦርድ ተወካዮች እና ተጋባዥ እንግዶችም ተገኝተዋል።
በመደበኛ ጉባኤው የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔ እንደሚያሳልፍም ይጠበቃል።
በጉባኤተኛው የፓርቲው እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ይቀርባል። ጉባኤተኛው የፓርቲው የደምብ ማሻሻያም ላይ ተወያይቶ የሚያጸድቅ ይሆናል።
በጉባኤው ፓርቲውን ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚመሩ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ ሥራ አስፈፃሚ አባላት እንዲሁም የፓርቲውን ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር እንደሚመርጥ ፓርቲው ለአሚኮ በላከው መግለጫ አስታውቋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleወጣቶች ከተቀጣሪነት ወጥተው ሥራ ፈጣሪነት ላይ ሊያተኩሩ ይገባል።
Next article‘’የተኩስ ድምፅ ሰልችቶናል’’ የደቡብ ወሎ ዞን ነዋሪዎች