
ደብረ ብርሃን: ኅዳር 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ መልዕክት በአማራ ክልል ደረጃ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በዓሉ በአማራ ክልል ከኅዳር አንድ ጀምሮ በተለያዩ መርሐ ግብሮች ሲከበር ቆይቷል።
በበዓሉ አከባበር ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ የጨፌ ኦሮሚያ፣ የአፋር ክልል እና የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር አፈ ጉባኤዎች እና የአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
