“የኢኮኖሚ ድርጅቶች መረጃ ስብሰባ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እና ደረጃ ለማወቅ የሚደረግ እንጂ ሌላ አላማ የለውም” የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት

31
አዲስ አበባ: ኅዳር 19/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ትክክለኛ መረጃ ለማሠባሠብ ይረዳው ዘንድ ለሕዝቡ መረጃ ለመስጠት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በጥቃቅን፣ አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ በሚሉ ዘርፎች ተከፍሎ እንደሚካሄድ በመግለጫው ተነስቷል።
የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ.ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አገልግሎቱ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ድርጅቶችን ቆጠራ እያካሄደ እና የተለያዩ መረጃዎችን እያሠባሠበ ነው ብለዋል።
ይህ የኢኮኖሚ ድርጅቶች መረጀ ስብሰባ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እና ደረጃ ለማወቅ የሚደረግ እንጂ ለሌላ አላማ የሚውል አለመኾኑን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
መረጃው የሀገሪቱን የአገልግሎት እና የምርት አቅም ለማወቅ ስለኾነ ዜጎች ለሚጠየቁት ጥያቄ ትክከለኛ መረጃ በመስጠት ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።
ዘጋቢ:- ረህመት አደም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየቋንቋ እና የባሕል ብዝኃነት ለሀገራችን ውበት እና መገለጫዎች ናቸው።
Next articleአካል ጉዳተኞችን ከተረጅነት በማላቀቅ የፖለቲካ ተሳትፏቸውን ማሳደግ ይገባል።