ጥምቀትን በጎንደር በድምቀት ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ ነው።

3

ጎንደር: ኅዳር 01/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ‎ጥምቀትን በጎንደር ለማክበር የሚመጡ ጎብኝዎችን በአግባቡ ለማስተናገድ በቂ ዝግጅት እየተደረገ መኾኑን የጎንደር ከተማ ዓለም አቀፍ ቅርስ አሥተዳደር አስታውቋል።

‎ጎንደር ከተማን ከሚያደምቋት በዓላት መካከል የጥምቀት በዓል አንደኛው ነው። ከተማዋ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን የያዘች መኾኗ ደግሞ ጎንደርን ተመራጭ ያደርጋታል።

‎‎አሁን ላይ የአብያተ መንግሥታቱ መጠገን የጎብኝዎችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም እንደሚያግዝ የጎንደር ከተማ አስጎብኝዎች ማኅበር አባል ሙሉቀን ተገኘ ተናግረዋል።

‎ወደ ታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ የሚመጡ ጎብኝዎችን በአግባቡ አስተናግዶ ለመሸኘት ዝግጁ መኾናቸውንም ነው የገለጹት።

‎ጎንደር ከተማን ከሌላው ጊዜያት ለየት የሚያደርጋት የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ የአብያተ መንግሥታቱ ጥገና መጠናቀቁ ነው ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ ዓለም አቀፍ ቅርስ አሥተዳዳሪ ጌታሁን ስዩም ናቸው።

‎ይህ መኾኑ ደግሞ ከተማዋን ልዩ ገጽታ አጎናጽፏታል ብለዋል። የጥምቀት በዓልን ተንተርሶ የሚመጡ ጎብኝዎችን በአግባቡ ለማስተናገድ በቂ ዝግጅት እየተደረገ መኾኑንም አንስተዋል።

‎‎የጎንደር አብያተ መንግሥታትን ለ24 ሰዓታት የማስጎብኘት ሥራ እየተሠራ መኾኑንም ገልጸዋል።

ዘጋቢ :- አዲስ አለማየሁ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአብያተ መንግሥታቱ ጥገና የጎንደርን የብርሃን ዘመን መልሷል።