ግብረ ገብነት የጎደላቸውን ነጋዴዎችን ማጋለጥ ይገባል።

5

ባሕር ዳር: ጥቅምት 20/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ‎የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር “ዘላቂ ሰላምን ለማጽናት የከፍተኛ እና የመካከለኛ ንግዱ ማኅበረሰብ ሚና” በሚል መሪ መልዕክት ከንግዱ ማኅበረሰብ ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።

‎የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኀላፊ ኃይለ ማርያም እሸቴ መድረኩ የከተማዋን ሰላም ለማስጠበቅ የሚመከርበት ነው ብለዋል።

‎ሰላም ከሌለ የንግድ ሥራ መሥራትም አስቸጋሪ በመኾኑ የንግዱ ማኅበረሰብ ጋር ስለ ሰላም መመካከር ያስፈልጋል ነው ያሉት።

‎የንግዱ ማኅበረሰብ ሰላሙን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን አላስፈላጊ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር ላይ ከመንግሥት ጎን ኾነው እንዲያግዙም ጠይቀዋል።

‎በአቋራጭ እና በአጭር ጊዜ ለማደግ በማኅበረሰቡ ላይ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ የኑሮ ውድነቱን ማባባስ እንደኾነ ነው የገለጹት። “ግብረ ገብ ያልኾኑ ነጋዴዎችን ማጋለጥ ይገባልም” ብለዋል።

‎የአካባቢን ሰላም በማስጠበቅ በኩል የንግዱ ማኅበረሰብም የበኩሉን እንዲወጣ መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎ዘጋቢ፦ ፍሬሕይወት አዘዘው

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየብልጽግና ፓርቲ ዓመታዊ ሥልጠናውን ማካሄድ ጀመረ።
Next articleየማኅበራዊ ሚዲያ እና የክላውድ ደኅንነት