‎”ብቁ ወጣት” የተሰኘ ፕሮግራም ይፋ ኾነ።

4

ባሕር ዳር: ጥቅምት 05/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ‎የአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) ከዩኒሴፍ እና ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር የሚተገብረውን ”ብቁ ወጣት” የተሰኘ ፕሮግራም የማስጀመሪያ መርሐ ግብር እያካሄደ ነው።

‎የአማራ ልማት ማኅበር ዋና ሥራ አሥፈጻሚ መላኩ ፈንታ ‎ፕሮግራሙ ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚተገበር እንደኾነ በመክፈቻው ላይ ተናግረዋል።

‎ፕሮግራሙ በሦስት ዓመት ውስጥ በክልሉ የሚገኙ ከ67 ሺህ በላይ ወጣቶችን፤ በአንድ ዓመት ውስጥ ደግሞ 23 ሺህ ወጣቶችን በአዕምሮ ጤና፣ በትምህርት፣ በክህሎት እና በሥራ ፈጠራ ዙሪያ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

‎በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

‎ዘጋቢ፦ ፍሬሕይወት አዘዘው

 

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

👇👇👇

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

 

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየባሕር ዳር – ጢስ ዓባይ አስፋልት መንገድ ግንባታ የት ደረሰ ? 
Next articleየሕግ የበላይነትን ለማስከበር የፖሊስ ተቋምን መቀላቀላችሁ የሚያስመሰግናችሁ ተግባር ነው።