አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ.ር) በጅቡቲ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኮነው ተሾሙ።

6

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 04/2018 ዓ.ም (አሚኮ) አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ.ር) በጅቡቲ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኮነው ተሾመዋል።

በጅቡቲ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኾነው የተሾሙት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ.ር) ከፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የሹመት ደብዳቤያቸውን በመቀበል ቃለ መሐላ ፈጸመዋል።

ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለተሿሚ አምባሳደሩ የኢትዮጵያ እና ጅቡቲን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ የሥራ መመሪያ ሠጥተዋል።

ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው በሥነ ሥርዓቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ.ር) እና ሌሎች የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየሞዴል አርሶ አደሮችን ተሞክሮ በማስፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየሠራ መኾኑን የጎንደር ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።
Next articleዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከጊዜ ወደ ጊዜ አቅሙን እያሳደገ መምጣቱን የአማራ ክልል ምክር ቤት አባላት ተናገሩ።