ሠንደቅ ዓላማችን የኅብረ ብሔራዊነታችን መገለጫ ነው።

6
ከሚሴ፡ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (አሚኮ) 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን ”ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችን እና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ መልዕክት በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል።
የኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ዋና አፈጉባኤ ፋጡማ ሞላ ሠንደቅ ዓላማችን የኅብረ ብሔራዊነታችን መገለጫ አርማችን ነው ብለዋል።
ሁሉም ሰው በተሰማራበት ሥራ ውጤት በማስመዝገብ ሀገሩን ሊጠብቅ ይገባል ነው ያሉት።
የብሔረሰብ አሥተዳደሩ አሥተዳዳሪ ተወካይ መሐመድ ሲራጅ የሀገራችንን ሉዓላዊነት በማስከበር የተከበረችና የታፈረች ሀገርን ለልጆቻችን ለማውረስ በትብብር መቆም ይገባናል ብለዋል።
ዘጋቢ:- ይማም ኢብራሒም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous article“በሀገራችን ሉዓላዊነት እና በሠንደቅ ዓላማችን ክብር ላይ አንደራደርም” ሌተናል ጀኔራል መሐመድ ተሰማ
Next articleየፍትሕ አገልግሎቱን ለማዘመን እየሠራ መኾኑን የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታወቀ።