“በሠንደቅ ዓላማ ፊት የገባነውን ቃል ጠብቀን ሀገራችንን ለቀጣይ ትውልድ እናስረክባለን” ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ

1
ጎንደር፡ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሀገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ የሠንደቅ ዓላማ ቀንን ‎”ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችን እና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ መልዕክት በልዩ ልዩ ወታደራዊ ትዕይንት አከብሯል።
‎የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ የሉዓላዊነት ተምሳሌት የኾነውን ሠንደቅ ዓላማ ከፍ ለማድረግ መስዋዕትነት የከፈሉ በርካታ ጀግኖች መኖራቸውን ተናግረዋል።
‎የቀደሙ ጀግኖች የውጭ ጠላቶችን ድል ነስተው ነጻነቷ የተረጋገጠ ሀገር ለትውልድ አስረክበዋል ብለዋል።
‎ሠንደቅ ዓላማ ለሠራዊቱ ትልቅ ትርጉም አለው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ “በሠንደቅ ዓላማ ፊት የገባነውን ቃል ጠብቀን ሀገራችንን በመጠበቅ ለቀጣይ ትውልድ እናስረክባለን፤ ሠንደቅ ዓላማውም ልዩ ትርጉም አለው” ነው ያሉት።
‎በኢትዮጵያ ከውጭም ከውስጥም ፈታኝ ሁኔታዎች ቢኖሩም የሠንደቅ ዓላማዋ ክብር ተጠብቆ ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገር ትቀጥላለች ብለዋል።
‎በሀገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አባላት የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማን ሲመለከቱ ሕዝብ፣ ሀገር፣ ነጻነት እና ኢትዮጵያዊነትን አንድ ላይ እንደሚያስቧቸው ጠቁመዋል። ሀገራቸውን በጽናት እንደሚጠብቁም ተናግረዋል።
‎በጀግንነት ነጻነቷ ተረጋግጦ የተረከቧትን ሠንደቅ ዓላማ ለትውልድ ለማስተላለፍ ያላቸውን ቁርጠኝነትም ገልጸዋል።
“‎ሀገር በመስዋዕትነት፣ በጀግንነት እና በድል ከፍ ትል ዘንድ በሠንደቅ ዓላማዋ ፊት ቃል ገብተናል” ነው ያሉት።
ዘጋቢ፦‎ቃልኪዳን ኀይሌ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleሠንደቅ ዓላማችን የአንድነታችን አርማ፣ የአብሮነታችን ቃል ኪዳን፣ የሀገራችን መገለጫ ምልክት ነው።
Next articleየተሠሩ የልማት ሥራዎች የከተማዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው።