የደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

11

ደብረማርቆስ፡ መስከረም 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል።

በጉባኤው የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት የልማት እና የመልካም አሥተዳደር ዕቅዶች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል።

በከተማው በመሠረተ ልማት ዘርፍ የተሠሩ ሥራዎች ክንውንን በመገምገም በተያዘው በጀት ዓመት ሊሠሩ የታቀዱ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ላይም ምክር ቤቱ ውይይት እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።

በጉባኤው የከተማው አሻጋሪ የዕድገት እና የዘላቂ ልማት ዕቅድም በከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ እንደሚቀርብ ይጠበቃል።

የከተማ አሥተዳደሩ የ2018 በጀት ድልድልም ለምክር ቤቱ ቀርቦ እንደሚጸድቅ ተመላክቷል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ዳኞች በዳኝነት ዕውቀት እና ሥነ-ምግባር ታንጸው ትክክለኛ እና ተገማች ውሳኔዎችን ማሳለፍ ይጠበቅባቸዋል” ዶክተር ምህረት ደበበ
Next article39 ሺህ የውጭ ዜጎች በሕገ-ወጥ ሰነድ ሲገለገሉ ተያዙ።