
ገንዳ ውኃ: መስከረም 17/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የመስቀል ደመራ በዓል በገንዳ ውኃ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
በዓሉ ሃይማኖታዊ ይዘቱን እና ትውፊቱን ጠብቆ ነው በድምቀት እየተከበረ የሚገኘው። ልዩ ልዩ ዝግጅቶች እና ያሬዳዊ ዜማም እየተከወነ ይገኛል።በበዓሉ ላይ የተለያዩ አድባራት ሊቃውንት፣ ዲያቆናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን፣ ካህናት እና ሕዝበ ምዕመኑ ታድመዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!