የመስቀል በዓል በሰላም እንዲከበር አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

8
ጎንደር: መስከረም 16/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ‎‎የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ የወንጀል መከላከል ምክትል መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ስማቸው አበበ በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ከማኅበረሰቡ ጋር በጋራ እየሠሩ መኾኑን ገልጸዋል።
‎በዓሉን በማክበር ሂደት ርችት እና መሰል የተከለከሉ ተግባራትን መፈፀም እንደማይቻልም አስታውቀዋል።
ወጣቶች ለሰላም ዘብ በመቆም ማገዝ አለባቸው ያሉት ኮማንደር ስማቸው ነዋሪዎች እንግዳ ነገር በአካባቢያቸው ሲመለከቱ ለጸጥታ ኀይል ጥቆማ እንዲሰጡም አሳስበዋል።
‎ኅብረተሰቡም ለጸጥታ ስጋት የኾኑ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ለጸጥታ አካላት ጥቆማ መሰጠት እንዳለበትም አሳስበዋል።
‎በዓሉ በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ በጋራ መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ዘጋቢ:- ‎ተስፋዬ ጋሹ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleየምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
Next article“ሕዝባዊ እና ሃይማኖታዊ በዓላት የኢትዮጵያ ብዝኃነት ማሳያ ናቸው” የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት