ቱጌዘር ዊ ለርን ኢትዮዽያ የተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

9
ጎንደር፡ መስከረም 09/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ቱጌዘር ዊ ለርን ኢትዮዽያ የተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት በጎንደር ከተማ ወላጆቻቸው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ 305 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።
ደብተር፣ እስክርቢቶ፣ እርሳስ፣ ቦርሳ እና የደንብ ልብስ ነው ድርጅቱ ድጋፍ ያደረገው።
ድጋፍ የተደረገላቸው የተማሪ ወላጆች ድርጅቱ ለልጆቻቸው ለትምህርት የሚያስፈልጉ የትምህርት ግብዓቶችን ድጋፍ ስላደረገላቸው አመሥግነዋል።
የቱጌዘር ዊ ለርን ኢትዮዽያ ሥራ አሥኪያጅ ታጠቅ እዘዘው ድርጅቱ በጎንደር ከተማ በ2018 የትምህርት ዘመን ያደረገው ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን ከ850ሺህ ብር በላይ እንደኾነም ገልጸዋል።
ዘጋቢ፦ ተስፋዬ ጋሹ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous article“በሕዳሴ የታየው ትዕምርታዊ ተግባር ሕዝቦችን ዋና ተሳታፊና ተጠቃሚ ያደረገ የላቀ የልማት አፈጻጸም ነው” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Next articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ.ር) ከመስከረም 9 ቀን ጀምሮ ለሁለት መሪዎች ሹመት ሰጡ።